የሀገር ውስጥ ዜና

የኢትዮጵያና ጅቡቲ የዕንባ ጠባቂ ተቋማት በጋራ ለመስራት ተስማሙ

By Meseret Demissu

October 22, 2020

አዲስ አበባ ፣ጥቅምት 12 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያና ጅቡቲ የእንባ ጠባቂ ተቋማት በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን መግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል።

የኢትዮጵያ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ዋና ዕንባ ጠባቂ ዶክተር እንዳለ ሃይሌ እና የጅቡቲ የዕንባ ጠባቂ ተቋም ዋና ዕንባ ጠባቂ ዶክተር ቃሲም ኢሳቅ ስምምነቱን ዛሬ ተፈራርመዋል።