አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 12፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የፌደራል ትራንስፖርት ባለስልጣን የሀገር ውስጥና የድንበር ተሻገር የጭነት ትራንስፖርትን በማዘመን የሀገሪቱን የወጪ ገቢ እንቅስቃሴ ቀልጣፍ፣ ምቹና ተወዳዳሪ እንዲሆን በኢ ሰርቪስ አገልግሎት አማካኝነት ዘርፉን በቴክኖሎጂ ለመደገፍ እየሰራ መሆኑን ገለፀ።
ቀደም ሲል የነበረው የኢ-ሰርቪስ አግልግሎት በአብዛኛው ማኑዋል ላይ የተመረኮዘ ከመሆኑም ባሻገር፥ የተደራሽነት እና ማዕከላዊ ዳታ ሲስተም ችግር የነበረበት በመሆኑ በአዲስ የኢ-ሰርቪስ አገልግሎት ማሻሻያ መደረጉንም ባለስልጣኑ አስታውቋል።