የሀገር ውስጥ ዜና

ከ13 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጡ ጥራታቸውን ያልጠበቁ የምግብ ምርቶች እና የሕክምና መሣሪያዎች ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ ታገዱ

By Feven Bishaw

October 23, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ከ13 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጡ ጥራታቸውን ያልጠበቁ የምግብ ምርቶች እና የሕክምና መሣሪያዎች ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ መታገዳቸውን የኢትዮጵያ የምግብ እና መድኃኒት ቁጥጥር ባለሥልጣን አስታወቀ።

ጥራታቸውን ያልጠበቁ የምግብ ምርቶች እና የሕክምና መሣሪያዎች ወደ ሀገር እንዳይገቡ የታገዱት በ2013 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት መሆኑ ተጠቁሟል።