የሀገር ውስጥ ዜና

የሕዝቦችን አንድነት ለመበተንና ሃገር ለመበጥበጥ የሚሰሩ ወንጀለኞችን መንግሥት አይታገስም – አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ

By Abrham Fekede

October 23, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሕዝቦችን አንድነት ለመበተንና ሃገር ለመበጥበጥ የሚሰሩ ወንጀለኞችን መንግሥት እንደማይታገስ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ ገለጹ፡፡

አፈ ጉባኤውና የመከላከያ ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙን ጨምሮ ከፍተኛ የፌደራልና የደቡብ ክልል አመራሮች በጉራፈርዳ ወረዳ ጥቃት ከደረሰባቸው የሕብረተሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት አድርገዋል።