የሀገር ውስጥ ዜና

ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት 25ኛ ዓመቱን ምክንያት በማድረግ የፓናል ውይይት ነገ ያካሄዳል

By Abrham Fekede

October 23, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት 25ኛ ዓመቱን ምክንያት በማድረግ ያዘጋጀው የፓናል ውይይት በነገው ዕለት ይካሄዳል፡፡

በፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት የኦፕሬሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሰጠኝ እንግዳው እንደተናገሩት የተቋሙ 25ኛ ዓመት አከባበር አካል የሆነው የፓናል ውይይት የተቋሙን ጉዞና አበርክቶ በመዳሰስ ባለፉት ጥንካሬዎች መነሻነት ተቋሙን የተሻለ ተወዳዳሪ ማድረግና ሀገራዊ ተልዕኮውን እንዲወጣ ማገዝን ያለመ ነው ብለዋል፡፡