አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 15፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን አስመልክተው የተናገሩት ግዴለሽ የሆነና ጥንቃቄ የጎደለው ንግግር በግድቡ ዙሪያ በመካሄድ ላይ ያለውን ድርድር የሚያኮላሽና በኢትዮጵያ፣ በግብጽና በሱዳን መካከል አላስፈላጊ ውጥረት እንዲፈጠር የሚያደርግ መሆኑ ተጠቆመ፡፡
በሰሜን ካሮላይና የእርሻና ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ ፕሮፌሰር የሆኑት ዶክተር ብሩክ ኃይሉ በሻህ እንደተናገሩት፤ የፕሬዚዳንቱ ንግግር ኢትዮጵያን፣ ሱዳንንና ግብጽን አላስፈላጊ ውጥረት ውስጥ የሚያስገባ ነው ብለዋል፡፡