የሀገር ውስጥ ዜና

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቅጥር ለመፈፀም ሁለት ቋንቋን መቻል የሚያስገድድ ህግ አልወጣም – አቶ ዣንጥራር አባይ

By Abrham Fekede

October 25, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 15፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሁለት ቋንቋዎችን እንደግዴታ ያስቀመጠበት ህግ እንዳላወጣ አስታወቀ፡፡

ቅጥርን በተመለከተ ከተማ አስተዳደሩ ሁለት ቋንቋዎችን እንደግዴታ አስቀምጧል እየተባለ የተናፈሱ መረጃዎች ከእውነት የራቁ መሆናቸውን በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት አስተባባሪ አቶ ዣንጥራር አባይ ገለጹ፡፡