TAMPA, FL - JUNE 25: A healthcare worker put on their personal protective equipment (PPE) before administering coronavirus tests to patients at the Lee Davis Community Resource Center on June 25, 2020 in Tampa, Florida. The USF Health system partnered with the Hillsborough County Government to provide coronavirus testing at several location sites throughout the county. Florida is currently experiencing a surge in COVID-19 cases, as the state reached a new record for single-day infections on Wednesday with 5,511 new cases. (Photo by Octavio Jones/Getty Images)

ኮሮናቫይረስ

በአሜሪካ በኮሮና ቫይረስ ለህልፈት የተዳረጉ ሰዎች ቁጥር ከ225 ሺህ አለፈ

By Abrham Fekede

October 26, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 16፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአሜሪካ በኮሮና ቫይረስ ህይወታቸውን ያጡ ሰዎች ቁጥር ከ225 ሺህ አለፈ፡፡

በቫይረሱ ከተጠቁ ሃገራት መካከል ዋነኛዋ በሆነችው አሜሪካ 8 ነጥብ 6 ሚሊየን ሰዎች በኮቪድ መያዛቸውን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡

ከ8 ነጥብ 6 ሚሊየን ሰዎች ውስጥ ከ3 ሚሊየን 422 ሺህ በላይ ሰዎች ማገገማቸውን የጆንሆፕኪንስ መረጃ ያመላክታል፡፡

በአሜሪካ በአንድ ቀን በቫይረሱ የሚያዙት ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ይገኛል ተብሏል፡፡

አርብ እና ቅዳሜ ብቻ ከ83 ሺህ በላይ ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል፡፡

እሁድን ጨምሮ ለሰባት ተከታታይ ቀናት የተያዙ ሰዎች በአማካይ ከ68 ሺህ በላይ ሲሆኑ ይህ ቁጥርም በሐምሌ ከተመዘገበው የሚልቅ መሆኑ ተገልጿል፡፡

በአሜሪካ አሁንም ጥንቃቄዎች ካልተደረጉ የሟቾች ቁጥር እንደሚጨምር ባለሙያዎች እየገለጹ ነው፡፡

ባለሙያዎቹ 95 በመቶ የሚሆነው ህዝብ ተገቢ በሆነ መንገድ የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ቢጠቀም የ100 ሺህ ሰዎችን ህይወት መታደግ ይቻል እንደነበር ገልጸዋል፡፡

 

ምንጭ፡-ሲ ኤን ኤን