የሀገር ውስጥ ዜና

የሶስትዮሽ ድርድሩ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅምና መብት ባስከበረ መልኩ ይካሄዳል – የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

By Abrham Fekede

October 26, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 16፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ነገ ከሰዓት ቀጠሮ በተያዘለት በህዳሴ ግድብ ላይ የሚያተኩረው የሦስትዮሽ ድርድር የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅምና መብት ባስከበረ መልኩ እንደሚካሄድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ድርድሩ ላይ የኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብጽ የውሃ ጉዳይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች እንደሚሳተፉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ተናግረዋል።