የሀገር ውስጥ ዜና

የአማራ ክልል መንግስት የፊታችን ረቡዕ በክልሉ የተለያዩ ከተሞች ለተጠራው ሰልፍ እውቅና አለመስጠቱን ገለጸ

By Feven Bishaw

October 26, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 16፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአማራ ክልል መንግስት የፊታችን ረቡዕ በክልሉ የተለያዩ ከተሞች ለተጠራው ሰላማዊ ሰልፍ እውቅና አለመስጠቱን አስታወቀ፡፡

የክልሉ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ግዛቸው ሙሉነህ ጉዳዩን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ በክልሉ የተለያዩ ከተሞች የፊታችን ረቡዕ ሰላማዊ ሰልፍ መጠራቱን አንስተዋል፡፡