አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 17፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በመተከል ዞን እየተስተዋለ ያለውን የጸጥታ ችግር በዘላቂነት ለመፍታት ከፌደራል መንግስት እና አጎራባች በሆኑት ክልል የተውጣጣው የከፍተኛ አመራሮች ግብረ ሃይል በህብረተሰቡ በኩል በተነሱ መሰረታዊ ጥያቄዎች ዙሪያ መፍትሄ ለማበጀት ያከናወናቸውን ስራዎች ገምግሟል።
በውይይቱ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ እና የመተከል ዞን ኮማንድ ፖስት ሰብሳቢ ኮሎኔል ወርቅነህ ጉደታን ጨምሮ የአማራ፣ የኦሮሚያ እንዲሁም የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከፍተኛ የፖለቲካ አመራሮች ተገኝተዋል።