የሀገር ውስጥ ዜና

የፌዴሬሽን ምክር ቤት የመረጃ አያያዝ ስርዓትን ለማዘመን የሚያስችለውን ውይይት አካሄደ

By Meseret Demissu

October 27, 2020

አዲስ አበባ ፣ጥቅምት 17 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የፌዴሬሽን ምክር ቤት የመረጃ አያያዝ ስርዓትን ለማዘመን የሚያስችለውን ውይይት ከፎረም ኦፍ ፌዴሬሽን ጋር አካሂዷል።

ምክር ቤቱ ከፎረም ኦፍ ፌዴሬሽን ጋር በመተባበር የፌዴራል ድጎማ እና የማከፋፈያ ቀመሮች ለማዘጋጀት የሚረዳ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈ የመረጃ አያያዝ ስርዓት ለመዘርጋት የሚያስችል ስራ ማስጀመሪያ ውይይት ነው ያካሄደው።