ኮሮናቫይረስ

በአውሮፓ በኮቪድ ምክንያት ለህልፈት የሚዳረጉ ሰዎች ቁጥር ካለፈው ሳምንት አንጻር 40 በመቶ ጨመረ

By Abrham Fekede

October 28, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 18፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአውሮፓ በኮቪድ ምክንያት በየዕለቱ ለህልፈት የሚዳረጉት ሰዎች ቁጥር ካለፈው ሳምንት አንጻር ሲታይ 40 በመቶ ገደማ መጨመሩን የዓለም ጤና ድርጅት አስታወቀ፡፡

የድርጅቱ ቃል አቀባይ ማርጋሬት ሃሪስ እንደገለጹት በፈረንሳይ፣ በስፔን፣ በብሪታንያ፣ በኔዘርላንድስ እና በሩሲያ በዋናነት ወረርሽኙ ስር የሰደደባቸው ሃገራት ናቸው፡፡