የሀገር ውስጥ ዜና

በደምቢዶሎ ተማሪዎችን አግተዋል በሚል የተጠረጠሩ ግለሰቦች ያቀረቡት የክስ መቃወሚያ ውድቅ ተደረገ

By Meseret Demissu

October 28, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 18፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በደምቢዶሎ ተማሪዎችን አግተዋል በሚል የተጠረጠሩ 17 ግለሰቦች ያቀረቡት የክስ መቃወሚያ ውድቅ ተደረገ።

ዐቃቤ ህግ በእነ ከሊፋ አብዱረህማን በሚጠራው የክስ መዝገብ በ17 ግለሰቦች ላይ በህዳር 24 እና 25 ቀን 2012 ዓ.ም ከአማራ ክልል የሄዱ ተማሪዎችን በመለየት ማገታቸውን ጠቅሶ የፀረ ሽብርተኝነትን አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀጽ 3/3 በመተላለፍ እንደ ወንጀል ተሳትፏቸው ሶስት ክስ ማቅረቡ ይታወሳል።