አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 18፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲዎች በሚመለሱበት ወቅት ለትራንስፖርት እና ለሌሎች ችግሮች እንዳይጋለጡ ቅድመ ዝግጅት መደረጉን የፌዴራል ትራንስፖርት ባለስልጣን አስታውቋል፡፡
በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ተቋርጦ የቆየውን ትምህርት ለማስቀጠል ሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረጋቸውን የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ይፋ ማድረጉ ይታወሳል፡፡