አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 19፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ 1 ሺህ 495ኛውን የነቢዩ መሐመድ የልደት በዓልን (መውሊድ) ምክንያት በማድረግ ኑሯቸውን በጎዳና ያደረጉ ዜጎችን በዛሬው ማዕድ አጋርተዋል።
ጎዳና ተዳዳሪዎቹን ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ፣ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት አስተባባሪ ከሆኑት አቶ ጃንጥራር አባይ ፣ የአዲስ አበባ ብልፅግና ጽህፈትቤት ኃላፊ አቶ መለሰ ዓለሙ እና የአዲስ አበባ ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተፈራ ሞላ መግበዋል።