የሀገር ውስጥ ዜና

የኦሮሚያ ቤተ ክህነት በሚል የተቋቋመው ኮሚቴ ያነሳቸው ችግሮች በጠቅላይ ቤተ-ክህነት እንዲፈቱ ዕርቅ ፈጸመ

By Meseret Demissu

October 29, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 19፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኦሮሚያ ቤተ ክህነት ለማቋቋም ሲሰራ የቆየው የኦሮሚያ ቤተ ክህነት አደራጅ ኮሚቴ ያነሳቸው ችግሮች በጠቅላይ ቤተ ክህነት ስር እንዲፈቱ ከቅዱስ ሲኖዶስ ጋር ዕርቅ መፈጸሙን ገለፀ።

ኮሚቴው ከጠቅላይ ቤተ-ክህነት ጋር የነበረው ልዩነት ባነሳቸው ችግሮች ሳይሆን በመፍትሔው ላይ እንደነበርም ተጠቅሷል።