የሀገር ውስጥ ዜና

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በንፁሃን ዜጐች ላይ በደረሰው ጥቃት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ገለጸ

By Abrham Fekede

November 02, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 23፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በምዕራብ ወለጋ ዞን ጉሊሶ ወረዳ ዋጋ ቃንቃ ቀበሌ በንፁሃን ዜጐች ላይ በደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ገልጻል፡፡

ምክር ቤቱ በፌስ ቡክ ገጹ ይህን መሰል ወንጀል በተደጋጋሚ እየተፈፀመ የዜጐች ህይወት እየተቀጠፈ ይገኛል ብሏል፡፡