Fana: At a Speed of Life!

በአዲስ አበባ አዋሬ ገበያ አካባቢ የተነሳው የእሳት አደጋ በቁጥጥር ስር ውሏል

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 25 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 በተለምዶ አዋሬ ገበያ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የተነሳው የእሳት አደጋ በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡

ከሌሊቱ 10 ሰአት አካባቢ የተነሳው የእሳት አደጋ በአዲስ አበባ ከተማ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የእሳት አደጋ መከላከል ባለሙያዎች፣ ፖሊሶች እና የአካባቢው ወጣቶች በቁጥጥር ስር መዋሉን የየካ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አስፋው ተክሌ ተናግረዋል፡፡

የእሳት አደጋው መንስኤ እና ያደረሰው ጉዳት በፖሊስ እየተጣራ መሆኑም ዋና ስራ አስፈጻሚ ገልጸዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና ከየካ ክፍለ ከተማ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በቦታው ተገኝተው የጉዳቱን መጠን በመመልከት ጉዳት የደረሰባቸውን ነዋሪዎች አጽናንተዋል፡፡

በእሳት አደጋው የደረሰውን ጉዳት እየተጣራ መሆኑንም ከአዲስ አበባ ፕሬስ ሴክሬታሪያት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.