የሀገር ውስጥ ዜና

ዶክተር አብርሃም በላይ የትግራይ ልዩ ሀይልና ሚሊሺያ በፌደራል መንግስትና በአማራ ክልል መንግስት የተደረገለትን የሰላም ጥሪ በሙሉ እምነት እንዲቀበል አሳሰቡ

By Abrham Fekede

November 04, 2020

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 25 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ህወሓት በአገራችን የመጣውን ለውጥ ተከትሎ በበርካታ ግጭቶች ውስጥ በስውርም ሆነ በግልፅ በአፍራሽ ተልእኮ እጁን ሲያስገባ ቆይቷል አሉ የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር ዶክተር አብርሃም በላይ፡፡

የህወሓት የጠላፊ ቡድን በትናንትናው ምሽት የሰላም ሀይል በሆነውና የትግራይ ህዝቦች ደጀን በመሆን ለአመታት ዋጋ እየከፈለ ባለው የአገር የመከላከያ ሰራዊት የሰሜን እዝ ላይ በወሰደው አሳፋሪ የጥቃት ትንኰሳና ዝርፊያ መነሻነት የፌደራሉ መንግስት መጠነ ሰፊ ህግ የማስከበር እርምጃ ለመውሰድ ተገድዷልም ብለዋል፡፡