ማይክ ፖምፔዮ በመከላከያ ሰራዊት ካምፕ ላይ የተፈፀመውን ጥቃት አወገዙ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 26፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፖምፔዮ በህወሓት ውስጥ ያለው ቡድን በመከላከያ ላይ ጥቃት መፈፀሙን አወገዙ፡፡
ሚኒስትሩ አካባቢው እንዲረጋጋና ሰላም እንዲወርድ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
በህወሓት ውስጥ ያለው ቡድን በትግራይ ክልል ውስጥ ባለ የመከላከያ ካምፕ ላይ ጥቃት መፈፀሙ የሚታወስ ነው፡፡
የፌደራል መንግስት የመከላከያ ሰራዊት ከአማራ ክልል የፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት ጥቃቱን በመመከት ወደ ማጥቃት መሸጋገሩን መግለፁ ይታወሳል፡፡