Fana: At a Speed of Life!

ኢንጂነር አዜብ አስናቀ ክስ ተመሰረተባቸው

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 17፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ የነበሩት ኢንጂነር አዜብ አስናቀ ክስ ተመሰረተባቸው።

በዚህ የክስ መዝገብ የቀድሞ የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ኮሎኔል ሙሉ ወልደ ገብርኤልን ጨምሮ 50 ሰዎች ይገኙበታል ተብሏል፡፡

ክሱ የተመሰረተው ከታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ጋር ተያይዞ በተካሄደ የደን ምንጣሮ ስራ ጋር ተያይዞ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

ኢንጂነር አዜብ አስናቀ በነሐሴ ወር 2010 ዓ.ም ከሀላፊነታቸው መነሳታቸው ይታወሳል።

ምንጭ፡- ኢዜአ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.