የሀገር ውስጥ ዜና

በቻይና እና ኢትዮጵያ መካከል ያለው ስትራቴጂካዊ ግንኙነት ተጠናክሮ ይቀጥላል – በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር

By Tibebu Kebede

December 27, 2019

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 17፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በቻይና እና ኢትዮጵያ መካከል ያለው ጠንካራ ስትራቴጂካዊ ግንኙነት በአዲሱ አመትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ታን ጂያን ተናግረዋል።

አምባሳደሩ የፈረንጆቹን አዲስ አመት አስመልክተው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፥ 2020 ቻይና እና ኢትዮጵያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩበት 50ኛ አመት በመሆኑ ልዩ ያደርገዋል ብለዋል።