የሀገር ውስጥ ዜና

ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ ለጆ ባይደን የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላለፉ

By Tibebu Kebede

November 07, 2020

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 28 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የአሜሪካ 46ኛ ፕሬዚዳንት ሆነው ለተመረጡት ጆ ባይደን የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላለፉ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትዊተር ገጻቸው ባሰፈሩት ፅሁፍ ዴሞክራቶቹን በመወከል የጆ ባይደን ምክትል ሆነው ለተመረጡት ካማላ ሀሪስም የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በመልዕክታቸውም ኢትዮጵያ ከባይደን አስተዳደር ጋር በቅርበት የመስራት ፍላጎት እንዳላት ገልጸዋል።