ኮሮናቫይረስ

በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 100 ሺህ ገደማ ደርሷል

By Abrham Fekede

November 09, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 30፣ 2013 (ኤፍቢሲ) በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ከገባ ጀምሮ በወረርሽኙ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 100 ሺህ ገደማ ደርሷል፡፡

ወረርሽኙ ወደ ኢትዮጵያ መግባቱ የተሰማው ባለፈው ዓመት መጋቢት 3 ቀን እንደነበር የሚታወስ ሲሆን አሁን ላይ 99 ሺህ 982 ሰዎች በወረርሽኙ መያዛቸው ነው የተገለጸው፡፡