አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 18 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በሳዑዲ ዓረቢያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ኢትዮጵያ እና ሳዑዲ ዓረቢያ በተፈራረሙት የሰራተኛ እና አሰሪዎች ስምምነት መሰረት ባለፉት ስምንት ወራት ከ11 ሺህ በላይ የቤት ሰራተኞችን ሰነድ ተቀብሎ ማስተናገዱን አስታወቀ።
በሳዑዲ ዓረቢያ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር አብዱላዚዝ አህመድ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደተናገሩት፥ ሰነዳቸው ከታየላቸው ሰራተኞች መካከል አብዛኛዎች ስራ ጀምረዋል።