የሀገር ውስጥ ዜና

አቶ ደመቀ መኮንን ከኬንያ ፕሬዝደንት ኡሁሩ ኬንያታ ጋር ተወያዩ

By Abrham Fekede

November 16, 2020

አዲስ አበባ፣ ህዳር 7፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከኬንያ ፕሬዝደንት ኡሁሩ ኬንያታ ጋር ተወያዩ።

በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የተመራ የኢትዮጵያ ልዑክ የቀጠናው ሀገራት መንግስት የጀመረውን ህግና ህገ መንግስት የማጽናት ጥረት እንዲደግፉ የጠቅላይ ሚንስትሩን መልዕክት ለፕሬዚዳንቱ አድርሰዋል።