“ለሀገር መከላከያ ክብር እቆማለሁ” መርሃ ግብር በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ተከበረ
አዲስ አበባ፣ ህዳር 8 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) “ለሀገር መከላከያ ክብር እቆማለሁ” መርሃ ግብር በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ተከብሯል።
በፕሮግራሙ ላይ የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ፣ አባ ገዳ እና ኡጋዞች እንዲሁም የሀገር ሽማግሌዎች በተጨማሪም የመንግስት ሰራተኞችና ባለጉዳዮች ለመከላከያ ሰራዊት ክብርና ምስጋና እንዲሁም ያላቸውን ድጋፍ መግለጻቸውን ከከተማ አስተዳደሩ ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።