Fana: At a Speed of Life!

የሕወሓት ጁንታ የትግራይ መሠረተ ልማቶችን እያፈረሰ ነው – አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 8 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የሕወሓት ጁንታ የትግራይ መሠረተ ልማቶችን እያፈረሰ መሆኑን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ አስታወቀ።

የመከላከያ ሠራዊት ወደፊት መገሥገሡ ያስጨነቀው ጁንታ፣ በሁሉም አቅጣጫ ወደ መቐለ በሚወስዱት መንገዶች ላይ የሚገኙ አራት ድልድዮች ማፍረሱንም ነው ያስታወቀው።

የተማመነባቸው ከባድ ምሽጎቹ ፈራርሰው፣ በሽሬ መንገድ የደረሰበት ሽንፈት ያንገበገበው ጁንታ፣ በሽሬና በአክሱም መካከል የሚገኘውን አስፓልት በግሬደር ቆፍሮ ወደ ጉድጓድነት ቀይሮታልም ነው ያለው።

የሕወሓት ጁንታ እስከዛሬ ከፈጸማቸው ወንጀሎች በተጨማሪ ባወደማቸው መሠረተ ልማቶች በቅርቡ ይጠይቅባቸዋልም ብሏል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.