ዓለምአቀፋዊ ዜና

በቻይና አንድ ህንፃ ላይ በደረሰ አደጋ የ6 ሰዎች ህይወት አለፈ

By Tibebu Kebede

December 30, 2019

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 19፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በደቡብ ምዕራብ ቻይና በአንድ ህንፃ ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ ስድስት ሰዎች ለህልፈት መዳረጋቸው ተሰማ፡፡

ቃጠሎው የደረሰ በደቡብ ምዕራብ ቻይና ቾንግኪንግ ማዘጋጃ ቤት ፍሊንግ አውራጃ ውስጥ ነው።

አደጋው አንድ የመኖሪያ ህንፃ ባደረሰው የእሳት አደጋ ምክንያት የተፈጠረ ሲሆን፥ ቢያንስ ለስድስት ሰዎች ሕይወት ህልፈት ምክንያት ሆኗል ነው የተባለው፡፡

ሆኖም እሳቱን ከአንድ ሰዓት በኋላ በቁጥጥር ስር ማዋል የተቻለ ሲሆን፥ የእሳት አደጋው መንስኤ እየተጣራ ይገኛል።

ምንጭ፦ ሲጂቲኤን