Fana: At a Speed of Life!

ጠ/ሚ ዐቢይ ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር አመራሮች ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 10 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር አመራሮች ጋር ተወያዩ።

በውይይቱ ወቅት የሕወሓት ጁንታ ከዚህ የባሰ ጥፋት ከማድረሱ በፊት በአስቸኳይ ለፍርድ እንዲቀርብ፣ የከተማው ሕዝብ እንዳይጎዳ ሕግ ለማስከበር በሚደረገው ዘመቻ በከተሞች አካባቢ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ ስምምነት መደረሱን የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት አስታውቋል፡፡

ከዚህ ባለፈም በጁንታው ግጭት ቀስቃሽነት ምክንያት የተፈናቀሉ ትግራዋይን ለመመለስና ለመርዳት በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር በኩል የተጀመረው ሥራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ውይይት ተደርጎ ስምምነት ላይ ተደርሷል።

ሕግ የማስከበር ዘመቻው ሲጠናቀቅ ትግራይን መልሶ ለማቋቋም የተዘጋጀው ዕቅድ በዝርዝር ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.