289 ኢትዮጵያውያን ዜጎች ከሳዑዲ ዓረቢያ ወደ ሃገራቸው ተመለሱ

By Tibebu Kebede

November 23, 2020

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 14 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) 289 ኢትዮጵያውያን ዜጎች በዛሬው እለት ከሳዑዲ ዓረቢያ ወደ ሃገራቸው ተመለሱ፡፡

ከተመላሾቹ መካከል 90ዎቹ ጨቅላ እና ታዳጊ ህጻናት መሆናቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ኢትዮጵያውያኑ መንግስት ከሳዑዲ ባለስልጣናት ጋር ባደረገው ትብብር ወደ ሃገራቸው የተመለሱ ናቸው፡፡