ስፓርት

ሎዛ አበራ የቢቢሲ 100 ተጽዕኖ ፈጣሪ ሴቶች ውስጥ ተካታለች

By Meseret Awoke

November 24, 2020

አዲስ አበባ፣ ህዳር 15፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) ሎዛ አበራ ዓለም ላይ በቢሲ ከተመረጡ 100 ተጽዕኖ ፈጣሪ ሴቶች መካከል አንዷሆና ተመርጣለች፡፡

ቢቢሲ በዚህ አመት ለውጥን የሚመሩ እና ለውጥ የሚያመጡ 100 ሴቶችን በዓለም ዙሪያ የመረጠ ሲሆን ሎዛ አበራ በስፖርቱ ዘርፍ ከ100ዎቹ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሴቶች አንዷ ሆናለች፡፡

ቢቢሲ በዕውቀት፣ በአመራርነት፣ በፈጠራ እና በማንነት ዘርፎች ውስጥ ተጽዕኖ ፈጥረዋል ያላቸውን ሴቶች ስም ዝርዝር ያወጣ ሲሆን ኢትዮጵያዊቷ የእግር ኳስ ተጫዋች ሎዛ አበራ ተካታለች፡፡

ሎዛ አበራ ከአሁን በፊት የተለያዩ እውቅናዎች እና ሽልማቶችን ማግኘቷ የሚታወስ ነው፡፡

ምንጭ፡- ቢቢሲ