የሀገር ውስጥ ዜና

ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ ከሳዑዲ ዓረቢያ ንጉስ ሠልማን ቢን አብዱል አዚዝ አል ሳኡድ ጋር ተወያዩ

By Tibebu Kebede

December 31, 2019

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 21፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢፌዴሪ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ ከሳዑዲ ዓረቢያ ንጉስ ሠልማን ቢን አብዱል አዚዝ አል ሳኡድ ጋር ተወያዩ።

ዶክተር ሙላቱ ተሾመ ከሳዑዲ ዓረቢያው ንጉስ እና የሁለቱ ቅዱሳን መስጊዶች የበላይ ጠባቂ ንጉስ ሠልማን ቢን አብዱል አዚዝ አል ሳኡድ በሪያድ ከተማ አል ያማማ ቤተ መንግስት በነበራቸው ቆይታም የኢትዮጵያና የሳኡዲ አረቢያ ሁለትዮሽ ግንኙነት በሚጠናከርበት ዙሪያ እንዲሁም በጋራ ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ መክረዋል።