Fana: At a Speed of Life!

የግብፁ ፕሬዚዳንት  ነገ በደቡብ ሱዳን ጉብኝት ሊያደርጉ ነው

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 18 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የግብጹ ፕሬዚዳንት አብዱል ፈታህ አል ሲሲ በነገው ዕለት በደቡብ ሱዳን ጉብኝት እንደሚያደርጉ  ተገለፀ።

ፕሬዚዳንት አብዱል ፈታህ አል ሲሲ በነገው ዕለት ጁባ የሚገቡ ሲሆን ከደቡብ ሱዳኑ ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ጋር ውይይት እንደሚያደርጉ ተነግሯል።

መሪዎቹ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት በተመለከተ እና ግንኙነቱን የበለጠ ማጠናከር በሚቻልበት ጉዳዮች ዙሪያ ይመክራሉም ነው የተባለው።

እንዲሁም በቀጠናዊ የፀጥታ ጉዳዮች ላይ ውይይት እንደሚያደርጉ  የደቡብ ሱዳን መንግስት አስታውቋል።

የአል ሲሲን ጉብኝት ታሪካዊ ነው ያለው የደቡብ ሱዳን መንግስት የጁባ ከተማ ነዋሪ ለፕሬዚዳንቱ አቀባበል እንዲያደርግም ጥሪ አቅርቧል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.