የሀገር ውስጥ ዜና

የኦሮሚያ ክልል መንግስት ካቢኔ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ

By Tibebu Kebede

December 31, 2019

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 21፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ካቢኔ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።

ካቢኔው በዛሬው እለት ባካሄደው ስብሰባው የባሌ ዞን በሁለት ዞኖች እንደ አዲስ እንዲደራጅ እና በሌሎች ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ በማሳለፍ እንዲጸድቁ ለጨፌ ኦሮሚያ መርቷል።