የሀገር ውስጥ ዜና

መስዋዕት ሆነው ኢትዮጵያን ወደፊት ላራመዱ ታሪክ ሰሪዎች ክብር ይገባል – ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል

By Tibebu Kebede

November 28, 2020

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 19፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) መስዋዕት ሆነው ኢትዮጵያን ወደፊት ላራመዱ ታሪክ ሰሪዎች ክብር እንደሚገባ የሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል ተናገሩ።

ሚኒስትሯ በህወሓት ጁንታ ላይ የተመዘገበውን ድል አስመልክተው የእንኳን ደስ አላችው መልዕክት አስተላልፈዋል።

በመልእክታቸውም ዘላለማዊ ክብር ኢትዮጵያን ከፍ ላደረጉ ጀግኖች ይገባል ብለዋል።

ሚኒስትሯ መቼም ከህሊናችን ለማትጠፉት የሰሜን ዕዝ የሰራዊቱ አባላት ክብር ይሁን ነው ያሉት።