ቢዝነስ

ኤክሳይዝ ታክስ ተጨምሯል የሚል የተሳሳተ ምክንያት አላስፈላጊ ዋጋ በሚጨምሩ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ ይወሰዳል

By Tibebu Kebede

December 31, 2019

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 21፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኤክሳይዝ ታክስ ተጨምሮብናል የሚል የተሳሳተ ምክንያት በማቅረብ በምርቶች ላይ አላስፈላጊ ዋጋ የሚጨምሩ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ እሸቴ አስፋው ገለፁ።

በአንዳንድ የፍጆታ ሸቀጦች ላይ ተጨማሪ የኤክሳይዝ ታክስ ተጥሏል የሚል የተሳሳተ ህብረተሰቡን በማደናገር የዋጋ ጭማሪ ማድረግ የጀመሩ ነጋዴዎች መኖራቸውን በዛሬው ዕለት የኤክሳይዝ ታክስ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በተካሄደው የፓናል ውይይት ላይ ተገልጿል።