Fana: At a Speed of Life!

በአፋር ክልል የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከታህሳስ 26 ቀን ጀምሮ ይሰጣል

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 25 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በአፋር ክልል የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከታህሳስ 26 እስከ 28 ቀን 2013 ዓ.ም እንደሚሰጥ የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ፡፡

የክልሉ ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ መሀመድ ሁመድ በክልሉ በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ተላልፎ የነበረው የ2012 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በተጠቀሰው ቀን እንደሚሰጥ ገልፀው÷ ተማሪዎች በቀሪ ጊዚያት እንዲዘጋጁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ፈተናውን የሚወስዱት በ271 የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ የሚገኙ 7 ሺህ 984 ተማሪዎች መሆናቸው ታውቋል፡፡

ከእነዚህ ውስጥም 4 ሺህ 837 የሚሆኑት ወንዶች፣ 3 ሺህ 147 ደግሞ ሴት ተፈታኞች መሆናቸውን ከክልሉ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤
ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል www.youtube.com/fanatelevision ሰብስክራይብ ያድርጉ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ
ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
611
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.