Fana: At a Speed of Life!

አየር መንገዱ ወደ መቐለ አቋርጦት የነበረውን በረራ ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 6፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ መቐለ አሉላ አባ ነጋ አውሮፕላን ማረፊያ አቋርጦት የነበረውን በረራ በዛሬው እለት በይፋ ጀመረ።

አየር መንገዱ በትግራይ ክልል በህወሓት ጁንታ ላይ ይወሰድ በነበረው የህግ ማስከበር ዘመቻ በረራውን አቋርጦ ቆይቷል።

ይሁን እንጂ የህግ ማስከበሩ ከተጠናቀቀ በኋላ በዛሬው እለት ምሽት ከአዲስ አበባ መንገደኞችን ጭኖ የመጀመሪያ በረራውን በማድረግ መቐለ አሉላ አባ ነጋ አውሮፕላን ማረፊያ ደርሷል።

ለመንገደኞችም የትግራይ ብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር ዶክተር አብርሃም በላይ፣ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር አባል ጀኔራል ዮሐንስ ገብረ መስቀልና የጊዜያዊ አስተዳደሩ አስተባባሪ አቶ ሃፍታይ ገብረ እግዚአብሔር አቀባበል አድርገውላቸዋል።

መቐለ የደረሰው አውሮፕላን ሌሎች መንገደኞችን አሳፍሮ ምሽቱን ወደ አዲስ አበባ መመለሱ ታውቋል።

የአውሮፕላን ማረፊያው ሰራተኞችም በስራ ገበታቸው ላይ የተገኙ ሲሆን፣ በቀጣይ አየር መንገዱ በቀን ሁለት ጊዜ የሚያደርገውን በረራ ይቀጥላል በመባሉን ኢዜአ ዘግቧል።

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤
ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ
ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
737
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.