የሀገር ውስጥ ዜና

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ በኢትዮጵያ ከፈረንሳይ አምባሳደር እና ልዑካን ቡድን ጋር ተወያዩ

By Feven Bishaw

December 17, 2020

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 8፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ፈጡም ሙስጠፋ በኢትዮጵያ ከፈረንሳይ አምባሳደር ሬሚ ማሬሾ እና ልዑካን ቡድን ጋር ተወያዩ፡፡

በውይይታቸውም የሃገራቱን ረጅም እድሜ ያስቆጠረ ታሪካዊ ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መክረዋል፡፡

በተጨማሪም በድሬዳዋ ያለውን ምቹ የኢንቨስትመንት እና የቱሪዝም አማራጮችን በመጠቀም የፈረንሳይ ባለሃብቶች በድሬዳዋ መዋዕለ ነዋያቸውን ማፍሰስ በሚችሉበት ሁኔታ ላይ መወያየታቸውን ከድሬዳዋ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤

ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል www.youtube.com/fanatelevision ሰብስክራይብ ያድርጉ

ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ

ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!