አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 23፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በትራንስፖርት ሚኒስትር ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ የተመራው የልዑካን ቡድን በሱዳን ካርቱም የነበረውን የስራ ጉብኝት በስኬት አጠናቋል።
ልዑኩ በካርቱም ቆይታውም ከሀገሪቱ የመሠረተ ልማትና ትራንስፖርት ሚኒስትር ኡመር አህመድ መሃመድ፣ የፖርት ሱዳን ኮርፕሬሽን ዋና ዳይሬክተር ካፕቴን አንዋር ሙሳ እንዲሁም ከንግድና፣ ከፋይናንስ ሚንስትርና ከጉሙሩክ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር ተወያይቷል።