የሀገር ውስጥ ዜና

በአማራ ክልል የ8ኛ ክፍል ክልል ዓቀፍ ፈተና እየተሰጠ ነው

By Tibebu Kebede

December 21, 2020

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 12 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል የ8ኛ ክፍል ክልል ዓቀፍ ፈተና መሰጠት ተጀመረ፡፡

ፈተናው በ5 ሺህ 162 ትምህርት ቤቶች እና የፈተና ጣቢያዎች እየተሰጠ መሆኑን የክልሉ ትምህርት ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ጌታቸው ቢያዝን ተናግረዋል፡፡

415 ሺህ 130 ተማሪዎች ለፈተና መቀመጣቸውንም ሃላፊው ገልጸዋል፡፡

በዚህም በመደበኛው 408 ሺህ 483፣ በማታው1 ሺህ 904 እንዲሁም በግል 4 ሺህ 743 ተማሪዎች ለፈተና ተቀምጠዋልም ነው ያሉት፡፡

ፈተናው ዛሬን ጨምሮ እስከ ታህሳስ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስ የሚሰጥ ይሆናል፡፡

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤ ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!