Fana: At a Speed of Life!

ዶክተር ሊያ ታደሰ በፈለገ ሕይወት ሆስፒታል የንፁህና ደህንነቱ የተጠበቀ ሆስፒታል የማድረግ እንቅስቃሴን ጎበኙ

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 19 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ በባህር ዳር በሚገኘው ፈለገ ሕይወት ሆስፒታል የንፁህና ደህንነቱ የተጠበቀ ሆስፒታል የማድረግ እንቅስቃሴን ጎበኙ፡፡

ሚኒስትሯ በተጨማሪም በኤሌክትሮኒክስ የታገዘ የጤና መዛግብት አፈፃፀም እና የአገልግሎት መስጫ ቦታዎች ህሙማንን ማዕከል ያደረጉ እንዲሆኑ ለማስቻል የተሰራውን ስራም ጎብኝተዋል፡፡

በጉብኝታቸው ወቅትም በቁርጠኝነት የሚሰሩ የሆስፒታሉንና የክልሉ ጤና ቢሮ አመራሮችንና ሰራተኞችን አመስግነዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.