የሀገር ውስጥ ዜና

ሀገር አቀፍ የሰላም ውይይት በአሶሳ ከተማ እየተካሄደ ነው

By Tibebu Kebede

January 06, 2021

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 28 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ከሀገር ሽማግሌዎች ጋር በመተባባር ያዘጋጀው ሀገር አቀፍ የሰላም ውይይት በአሶሳ ከተማ እየተካሄደ ነው።

ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከተውጣጡ የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር የሚካሄደው ውይይት በአካባቢው እና በሀገሪቱ ፀጥታ ጉዳይ ላይ ያተኮረ ነው ተብሏል።

ለአንድ ቀን በሚቆየው በዚሁ ውይይት የተለያዩ ሃይማኖት ተቋማት እና ከፍተኛ አመራሮች ተሳታፊዎች መሆናቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ውይይቱን የሰላም ሚኒስቴር እና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሰላም ግንባታ እና ፀጥታ ቢሮ በጋራ አዘጋጅተውታል፡፡

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤ ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!