የሀገር ውስጥ ዜና

ተጨማሪ 300 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ሲያዙ የዘጠኝ ሰዎች ህይወት አልፏል

By Tibebu Kebede

January 11, 2021

አዲስ አበባ ፣ ጥር 3 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ ለ4 ሺህ 599 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 300 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸውን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።

በአጠቃላይ እስካሁን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 128 ሺህ 616 ደርሷል።

በሌላ በኩል 189 ሰዎች ከቫይረሱ ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ እስካሁን ድረስ 113 ሺህ 563 ሰዎች ከቫይረሱ አገግመዋል።

በተያያዘም በትናንትናው እለት የዘጠኝ ሰዎች ህይወት ያለፈ ሲሆን፥ እስካሁን በቫይረሱ ሳቢያ 2 ሺህ 3 መድረሱም ተገልጿል።

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤ ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!