የሀገር ውስጥ ዜና

በስልጤ ዞን ጦራ ከተማ የደረሰ የእሳት አደጋ ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ንብረት አወደመ

By Tibebu Kebede

January 14, 2021

አዲስ አበባ ፣ ጥር 6 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በስልጤ ዞን ጦራ ከተማ ከተማ ትናንት ምሽት የደረሰ የእሳት አደጋ ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ማውደሙን ፖሊስ አስታወቀ፡፡

የጦራ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አዛዥ ሳጅን ሬድዋን ደኑር የአደጋው መንስኤ ኤሌክትሪክ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

እሳቱ ተጨማሪ ጉዳት ሳያደርስ በህብረተሰቡ ከፍተኛ ርብርብ መጥፋቱንም ገልጸዋል፡፡

በመጨረሻም መሠል አደጋዎች እንዳይደርሱ ህብረተሰቡ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበት መልዕክት ማስተላለፋቸውን ከስልጤ ዞን ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤ ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!