የሀገር ውስጥ ዜና

ዘመናዊ የከተማ ግብርናን ለማስፋፋት በአነስተኛ ቦታ የሚሰሩ የአትክልት እና የፍራፍሬ ስፍራዎች ወሳኝ ናቸው- ወ/ሮ አዳነች

By Tibebu Kebede

January 16, 2021

አዲስ አበባ፣ ጥር 8፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ዘመናዊ የከተማ ግብርናን ለማስፋፋት በአነስተኛ ቦታ የሚሰሩ የአትክልት እና የፍራፍሬ ስፍራዎች ወሳኝ መሆናቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

ገበያን በማረጋጋትና የኑሮ ውድነትን ለመቀነስም ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው አስታውቀዋል።

ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ዛሬው ዕለት ከትምህርት ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ጌታሁን መኩሪያ ጋር በኢትዮጵያ ደረጃዎች ኤጀንሲ የተሰራ ዘመናዊ የከተማ ግብርና ማሳያን ጎብኝተዋል።

ይህን መሰል በአነስተኛ ቦታ የሚሰሩ የአትክልት እና የፍራፍሬ ስፍራዎች ገበያን በማረጋጋትና የኑሮ ውድነትን በመቀነሱ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ስላላቸው ፣ ዘመናዊ የከተማ ግብርናን ለማስፋፋት ለምንሰራው ስራ እንደተሞክሮ መውሰድ የሚያስችል ሆኖ አግኝተነዋል ብለዋል።

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤ ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!