የሀገር ውስጥ ዜና

አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ከዩኒሴፍ ዋና ዳይሬክተር ሄንሪታ ፎር ጋር ተወያዩ

By Tibebu Kebede

January 22, 2021

አዲስ አበባ ፣ ጥር 14 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ከዓለም አቀፉ የህጻናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) ዋናዳይሬክተር ሄንሪታ ፎር ጋር ተወያዩ፡፡

በውይይታቸው ወቅትም በትግራይ ክልል የሰብዓዊ እርዳታ ማስተባበሪያ ማዕከል ማቋቋም በሚቻልበት አግባብ ላይ መምከራቸውን አስታውቀዋል፡፡

ከዚህ ባለፈም ተጨማሪ አልሚ ምግቦችና የህክምና ቁሳቁስ ማቅረብ በሚቻልበት አግባብ ላይም መወያየታቸውን ገልጸዋል፡፡

እንዲሁም እርዳታና የህክምና ቁሳቁሶችን በፍጥነት ማድረስ በሚቻልበት አግባብ ላይም ተወያይተዋል፡፡

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤ ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!