አዲስ አበባ፣ ጥር 23፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) 38ኛው የጃንሜዳ አለማቀፍና ሀገር አቋራጭ ውድድር በፊንፊኔ ዙሪያ የኦሮሚያ ልዩ ዞን ሱሉልታ ከተማ ተካሂዷል።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በሱሉልታ ከተማ ባዘጋጀው በዚህ ውድድር ላይ ከ7 ክልልች የተውጣጡ አትሌቶች የተሳተፉ ሲሆን በውድድሩ ላሸነፉ አትሌቶች ከ750 ሺህ ብር በላይ ሽልማት ተሰጥቷል።
ዕድሜያቸው ከ50 ዓመት በላይ የሆኑ አትሌቶች በውድድሩ ተሳትፈዋል።
በሀገር አቋራጭ ወጣት ሴቶች በ6 ኪሎ ሜትር ፥ ወጣት ወንዶች ደግሞ በ8 ኪሎ ሜትር ተወዳድረዋል።
በውድድሩ ከ1ኛ አስከ 8ተኛ ለወጡ አሸናፊዎች ሽልማት ተሰጥቷል።
ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤
ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ
ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!